Earn on crypto without
self-trading
We manage the capital and take a percentage only from profits.
Strategy, risk management, constant market monitoring.
LEARN MORE

Kalon


@penchantforkalonandmetanoia

Latest publications


Kalon
Publication date: 22 Apr, 16:23

👁 34 👍 2 💬 0 🔁 1
Kalon
Publication date: 21 Apr, 20:37
ትናንት አንድ ያስገረመኝን ጸሎት ሰማሁኝ (ሰውዬው ወዳጅ ባለው ሰው ተጎሶሞ ነው) "ጌታ ሆይ ይህ ነገር አንተ ያስመለጥከኝ ወጥመድ ከነበረ ተመስገን፣ ነገር ግን ይህ ሰው ንጹህ እያለ ከእኔ ድካም የተነሳ ጠርጥሬው ከሆነ ምህረትን አድርግልኝ።" አንድም ቀን ሰውን አለማመን ሃጢያት ሆኖ ንስሃ ያስገባል ብዬ አስቤ አላውቅም። ዘመናችንም ቢሆን አዳኝ ከቧት እንደምትኖር ታዳኝ በንቃትና በብልጠት ለሚንቀሳቀስ እንጂ ለማይጠረጥር አማኝ ቦታ ያለው አይመስልም። እንደውም  አሰልጥኗቸው ወደ አጥቂነት ለሚደርሱ ኢ-ታማኞች ሸላሚ አለም ይመስላል። እምነትና ፍቅር አብረው የሚሄዱ ነገሮች ናቸው ብዬ አስባለሁ። የማንወደውን አካል ማመን የሚከብድ ነገር ነው። በ1ኛ ቆሮ 13 ላይ ከተገለጸው የፍቅር መልክ አንዱ ሁሉን ማመን ነው። ምን ማለት ይሆን ሁሉን ማመን? ጋሽ ንጉሴ ቡልቻ ይህ ቃል ለእሳቸውም ትንሽ ለመፍታት እንደሚያስቸግራቸው ከገለጹ በኃላ፦ ሁሉን ያምናል ማለት ፍቅር ያለ ቅድመ ፍርድ ሰውን የመቀበያ ሰፊ ልብ አለው ማለት ነው ሲሉ ገለጹት (በእኔ አጻጻፍ)። መልካም ፍቺ ነው በእውነቱ። በአዲስ አበባ ምድር ግን ሰውን ማመን ከኑሮ በላይ የከበደ ነገር እየሆነ ነው። በዚህ ከቀጠልን እዚህ ሃገር ማርጀት (ዳ ብሎ መኖር) ላይቻል ነው። "ያልጠረጠረ ተመነጠረ" እያለ በሚተርት ህዝብ መሃል ሁሉን በልበ ሰፊነት የሚቀበል (የሚያምን) ሰው መሆን ከባድ ለመሆኑ የአይን ምስክር ከሆንኩ ሰነባበትኩ። ጥያቄዬ፦ በየቀኑ ልብ አጥባቢ ጨካኞችን በምናይበት ከባቢ ላይ በየት በኩል ልባችን ሰፍቶ ፍቅርን እንኑረው የሚል ነው? ገጠመኝ ላክላችሁ😊 አንድ እሁድ ከሰዓት ነው። በወቅቱ ህብረት አደርግበት ከነበረው ቤተ ክርስቲያን እሁዴን ቀድሼ እየወጣሁ እያለ የግቢ የቴሌግራም ቻነል ላይ ጸዴ በሆነ ርዕስ ላይ የተደረገ ፖድካስት ተለቆ አየሁኝ። እንዲያ ከሆነማ ታክሲ ከምይዝ ይህን እየሰማሁ ላዝግም ብዬ የጆሮ ማዳመጫዬን ደቅኜ ከህዝቡ ይልቅ አምሮ የተነጠፈውን የሃገሬን አስፋልት እፈጨው ጀመር። ነፋሻማው አየር ውሳኔየን ልክ መሆኑን ሊያሳምን እየተጋ ነው። ደሊቨሪ የሚሰሩ ሃብታም ብስክሌት አሽከካሪዎች ባጠገቤ ያልፋሉ፣ ውጪ ሃገር እንጂ ሃገሬ ውስጥ ይኖራሉ ብዬ የማላስባቸው አደገኛ ውሾችን ለመጀመሪያ ጊዜ እያየሁ ነው። በመሃል አንድ ሰው ከኃላዬ ሆኖ እየጠራኝ መሆኑን አስተዋልኩ። ዞር ብዬ "አቤት ምን አሉኝ" አልኩኝ። አጠርና ወፈር ያሉ አባት ናቸው። ከጸሃዩአ የማይመስል ላብ በላያቸው ላይ ሰፏል። እንዲህ እየሞቃቸውም ግን ትልቅ ጃኬት አድርገዋል። "ወረዳ 13 የት እንደሆነ ታውቃያለሽ የኔ ልጅ" “አይ አላውቀውም ሌላ ሰው ይጠይቁ” አልኳቸውና መንገዴን ቀጠልኩኝ። ነገር ግን ለእኒህ ሰው ደግ መሆን እንዳለብኝ ተሰማኝ። አይደለም ስሰበክ ውዬ ይቅርና እንዲሁም ሩሩህ ነኝ🙂‍↔️። ወዲያውኑ ዞር ብዬ ሳያቸው ማንንም እየጠየቁ አልነበረም። ግራ የተጋቡ የክፍለ ሃገር ከመምሰላቸው ባለፈ በቃ ሁሉ ነገራቸው አንጀት ይበላል። እንዳለመታደል ሆኖ ያን ቀን አንጀቴን ራሃብ ቀድሞ በልቶት ነበር። ልብ ግን ነበረኝ🤧 ስለዚህ ተመልሼ ተጠጋኋቸውና “እኔ ልጠይቅሎት?” ብዬ ጠየኳቸው። “አይ ተይው የኔ ልጅ ተይው” አሉኝ። “ኧረ ምንም ችግር የለውም” ብዬ አካባቢው ላይ የነበሩትን ሰዎች ጠየኩላቸው እናም ጠቆሙን። ከዛም መንገዴን ቀጠልኩኝ። ለካ ቦታው ጥቂት ያህል አብረን ያስኬድ ስለነበረ አብረን መሄድ ጀመርን። “ይገርምሻል ማንኛውም የቀበሌ መታወቂያ ያለው ሰው ነጻ ስኳርና ዘይት መውሰድ ይችላል ተብዬ ነውኮ። ሰዉ ደግሞ መናገር አይፈልግም እንጂ መሰጠት ከተጀመረ ሳምንት አለፈው ዛሬ የመጨረሽ ቀን ነው ተብሏል። ምቀኛ ምቀኞች ነን።” ሁሉም ነገር የእይታ ጉዳይ ነው ብዬ አምናለሁ። ለምሳሌ የኢትዮጲያን ህዝብ እንውሰድ፦ የኢትዮጵያ ህዝብ ከሀብታሞች አንግል ሁሌም ደግና ሩሩህ ህዝብ ሲሆን ከድሆች አንግል ደግሞ አስመሳይ ምቀኛና ሸረኛ ነው። “አይደለ! አይ በመጨረሻም ቀን ቢሆን ይደርሶታል ይቅናዎት መልካም እድል” ብያቸው ወደ ፖድካስቱ ሃሳቤን ለመመለስ ሞከርኩኝ። ትንሽ ሰኮንዶች እንዳለፉ ነጠላ ያደረገች አንዲት ወጣት ተቀላቀለችንና ሰላም ተባባሉ። ከወሬያቸው እሷም ወደ ወረዳ 13 እየሄደች እንደሆነና ትውውቃቸውም ወረዳው ላይ የነበረው የቅዳሜ ሰልፍ እንደሆነ ለመረዳት ቻልኩኝ። ቅን ልጅ ትመስላለች። “ዛሬማ እንደምንም ብለን እንቀበላለን። እኛ የት ሄደን እንኑር? ደግሞኮ ለደሃ ከመጣው ጋር ሃብታሞች እኩል አብረውን ሲጋፉ መዋላቸው ነውኮ የሚገርመኝ...” ትላለች። እውነቷን ነው በዚህ ዘመን ማንም በቃኝ አይልም። ስግብግቦች ነነ! የስግብግብነት መነሻ ምን ይሆን? ብዬ እያሰብኩ እያለ BOOM “ለምን አብረሽን አትሄጅም?” የሚል ግብዣ ከልጅቷ ዘንድ መጣ። በወቅቱ አክስቴ ጋር ነበር የምኖረው። እናም አይደልም ስለስኳርና ስለዘይት ላስብ ቀርቶ ቤት ውስጥ የስኳር እቃው የት እንዳለ ራሱ አላውቅም ነበር። “አይ አያስፈልገኝም አመሰግናለሁ።” ብዬ ከፈገግታ ጋር መለስኩኝ። “እንዴ ለምን ኪሎ ስኳር ስንት እንደገባ ሰምተሻል? ዘይቱማ አይነገርም። እንዴት አትፈልጊም ግን? ከሃብታሞቹ ጎራ ነሽ እንዴ?” ኤፍራታ ምን ትወስን ይሆን🤔? ክፍል 2 ይቀጥላል
👁 63 👍 4 💬 0 🔁 1
Kalon
Publication date: 18 Apr, 16:02

Go out and get some fresh air😊
👁 120 👍 5 💬 0 🔁 0
Kalon
Publication date: 16 Apr, 12:06

Media file
👁 134 🔁 1
Kalon
Publication date: 16 Apr, 12:06

Media file
My mind before adulting vs. my mind after😄
👁 133 👍 8 💬 0 🔁 1
Kalon
Publication date: 14 Apr, 14:51
Someone said "ቅድስና የእግዚአብሔር ምርጫ ውጤት እንጂ የመመረጫ መስፈርት አይደለም።"
👁 163 👍 9 💬 0 🔁 0
Kalon
Publication date: 13 Apr, 14:43

Media file
👁 168 👍 3 💬 0 🔁 0
Kalon
Publication date: 13 Apr, 09:32
Less love = more expectation More love = less expectation ነው አለ አንዱ tiktok ላይ። ሰው ፍቅሩ ትንሽ ሲሆን expectationኑ ብዙ ነው። በጣም ሲወድ ግን ምንም expect አያደርግም። እንደውም ከሙላቱ ለማካፈል ብቻ ይጥራል። እናም ይህን የtiktok video ሳይ የመጣልኝ ሀሳብ፡ በገነት ለመኖር መፈጠራችን + በነጻ/በጸጋ መዳናችን እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ወደር አልባ ፍቅሩን ያሳያል ብል ያስኬደኛል ማለት ነው ብዬ አሰብኩ። ይህ ሀሳብ ባለፈው አንድ group discussion ላይ የሆነች ልጅ ያነሳችውን ጥያቄ አስታወሰኝ "እግዚአብሔር ለምን ሰውን ፈጠረ? (since you're saying 'እግዚአብሔር ሁሉን ያውቃል' ሰው እንደሚወድቅም እያወቀ፣ ወደዚህ ክፉ አለም ልጁን እንደሚያስልክለው እያወቀ፣....ለምን ፈጠረን?)" ይህን ተከትሎ ያልተነሳ ጥያቄና መልስ አልነበረም በእውነት። i really enjoyed it!! ያስማማን መልስ እግዚአብሔር እኛን ብቻ ሳይሆን ፍጥረትን ሁሉ ሲፈጥር "በሥላሴ መሃል የነበረውን ፍቅርና ክብር ለማካፈል ነው" የሚል ነበር። አጋፔ የሆነው ፍቅሩም ያለኛ መዋጮ ለክብሩ እንድንድን ምክንያት ሆኗል ብለን ቋጨነው። So, more love = less expectation🙂
👁 158 👍 11 💬 0 🔁 0
Kalon
Publication date: 11 Apr, 19:37
የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የመታዘዝ እድሜውን÷ ህማማቱን÷ ስቃዩን÷ ሞቱንና ትንሳዔውን ስታስቡ ለነበራችሁ ሁሉ መልካሙን መረጣችሁ ከእናንተም አይወሰድባችሁ እያልኩኝ ምርቃት ቢጤ ላክላችሁ: እግዚአብሔር ሞተ ያላችሁትን ነገራችሁን  ይቀስቅስላችሁ÷ ለፍርሃታችሁ ማምከኛ የሚሆን አጽኚ ቃል ከጆሯችሁ አይለይ÷ የለገመባችሁ እንቅፋት ከፊታችሁ ገለል ይበልላችሁ÷ ስህተታችሁን የማረሚያ እድል አትነፈጉ÷ ትከሻችሁ ከኃላፊነታችሁ አይነስባችሁ÷ ከእግዚአብሔር ሀሳብ ጋር ከመተላለፍ ተከለሉ÷ የእግዚአብሔርን የሚያስንቅ እውቀት ከእናንተ ይራቅ÷  መልካሙን ለማየት አይኖቻችሁ ይንጹላችሁ÷ በቅንነት የዘራችሁት አምሮ ለምልሞ ወደ ጎተራችሁ ይግባ÷ ለጠላት በሚታይ ቅጥር ተከበቡ... እንኳን ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ🤗
👁 173 👍 13 💬 0 🔁 0
Kalon
Publication date: 01 Apr, 06:49

👁 249 👍 4 💬 0 🔁 0